የስቴት እና የአካባቢ መስተዳድር የሳይበርሴኩሪቲ ድጎማ ፕሮግራም (SLCGP)​

በሴፕቴምበር 16 ቀን 2022 ዓ.ም የሀገር ውስጥ ደኅንነት መምሪያ (DHS) በመላው ሀገሪቷ ለሚገኙ የስቴት፣ የአካባቢ መስተዳድር እና ግዛታዊ (SLT) መንግሥታት የሚያገለግል በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነውን የሳይበርሴኩሪቲ ድጎማ ፕሮግራም ይፋ አድርጓል።​​​

VITA ከኮመንዌልዙ የስቴት አስተዳደር ኤጀንሲ (SAA) እና የVirginia የአደጋ ጊዜ አስተዳደር መምሪያ ጋር በመተባበር ክፍት ለሆኑት የፕሮግራም ዓመታት በሙሉ ማመልከቻ አስገብቶ ተቀባይነት ማግኘት ችሏል።​

​Virginia በSLCGP ውስጥ የምታደርገው ተሳትፎ የሚከተሉት ላይ የሚያተኩር ነው፦​

  • በተጫለ መጠን ለበርካታ አካላት ማሻሻያዎችን ማሳካት​

  • ከፌደራል የድጎማ ፕሮግራሙ ጋር የተያያዘው የገንዘብ ድጋፍ ዕድሎች ማሳወቂያ ውስጥ የተቀመጡትን መስፈርቶች እያሟሉ መሳተፍ እንዲችሉ ብቁ ለሆኑ አካላት ሂደቱን ማቃለል።​

እነዚህ ሁለት የትኩረት አቅጣጫዎች የሚከተሉት ገጽታዎች ያሉት የፕሮግራም ንድፍ ፈጥረዋል፦​

  • ብቃት ያላቸው አካላት የፌደራል ድጎማ አስተዳደር መስፈርቶችን ጫና መሸከም ሳይኖርባቸው መሳተፍ የሚችሉበትን ዕድሎች ያቀርባል​

  • ድጋፍ የሚያደርግ የሰው ኃይል ላይኖራቸው ለሚችሉ ብቁ የሆኑ አካላት ማሻሻያዎችን ለመተግበር እና ለማስተዳደር አስፈላጊ የሆኑትን ግብዓቶች የሚያቀርቡ የአፈጻጸም ዓይነቶችን ይፈጥራል​

  • በአንፃሩ ቀላል​የሆኑ መተግበሪያዎችን ያካትታል

Virginia ለSLCGP ያላት አቀራረብ ከበርካታ የድጎማ ፕሮግራሞች አንፃር የተለየ ቢሆንም፣ በSLCGP የገንዘብ ድጋፍ ዕድሎች ማሳወቂያ ውስጥ በተዘረዘሩት ዓላማዎች አማካኝነት ሥርዓታዊ የሳይበር ስጋቶችን ለመቆጣጠር እና ለመቆነስ በቁርጠኝነት ይሠራል።​

የፌደራል SLCGP ፕሮግራም ዙሪያ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት https://www.cisa.gov/cybergrants/slcgpን ይጎብኙ።​

የግዛት እና የአካባቢ የሳይበር ደህንነት ስጦታ ፕሮግራም (SLCGP) ተደጋጋሚ ጥያቄዎች

መጨረሻ የዘመነው ፡ ጥር 8 ፣ 2025